የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ 84 ሺህ 659 የሚገመቱ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህጻናት ምንም አይነት የትምህርት አገልግሎት እያገኙ እንዳልሆነ አስታውቋል፡፡ ዩኒሴፍ ትናንት የሰጠውን መግለጫ ጠቅሶ አናዶሉ ኤጀንሲ እንደዘገበው፣ በሁለቱ ክልሎች የተከሰቱ ግጭቶች 14 ሺህ ያህል ህጻናትን ከወላጆቻቸው ጋር እንዲለያዩ ምክንያት ሆነዋል ተብሎ ይገመታል፡፡
በሁለቱም ክልሎች 120 ሺህ የሚገመቱ ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆናቸው ህጸናት እንዲሁም 20 ሺህ ነፍሰ ጡርና ጡት የሚያጠቡ እናቶች የአሰቸኳይ የንጥረምግብ አገልግሎቶች ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ያለው ዘገባው፣ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱትን ህጻናት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት እንዲያገኙ ለማስቻል 2.9 ሚሊዮን ዶላር ያህል እንደሚያስፈልግ ዩኒሴፍ ማስታወቁን አመልክቷል፡፡
Saturday, 06 January 2018 12:10
በኦሮሚያና ሶማሌ የተፈናቀሉ 85ሺህ ያህል ህጻናት ትምህርት አያገኙም ተባለ
Written by Administrator
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል