Print this page
Saturday, 06 January 2018 12:10

በኦሮሚያና ሶማሌ የተፈናቀሉ 85ሺህ ያህል ህጻናት ትምህርት አያገኙም ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ 84 ሺህ 659 የሚገመቱ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ህጻናት ምንም አይነት የትምህርት አገልግሎት እያገኙ እንዳልሆነ አስታውቋል፡፡ ዩኒሴፍ ትናንት የሰጠውን መግለጫ ጠቅሶ አናዶሉ ኤጀንሲ እንደዘገበው፣ በሁለቱ ክልሎች የተከሰቱ ግጭቶች 14 ሺህ ያህል ህጻናትን ከወላጆቻቸው ጋር እንዲለያዩ ምክንያት ሆነዋል ተብሎ ይገመታል፡፡
በሁለቱም ክልሎች 120 ሺህ የሚገመቱ ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች የሆናቸው ህጸናት እንዲሁም 20 ሺህ ነፍሰ ጡርና ጡት የሚያጠቡ እናቶች የአሰቸኳይ የንጥረምግብ አገልግሎቶች ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ያለው ዘገባው፣ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱትን ህጻናት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት እንዲያገኙ ለማስቻል 2.9 ሚሊዮን ዶላር ያህል እንደሚያስፈልግ ዩኒሴፍ ማስታወቁን አመልክቷል፡፡

Read 2820 times
Administrator

Latest from Administrator