Print this page
Monday, 15 January 2018 00:00

ትራምፕ ከናይጀሪያ የተዘረፈውን ግማሽ ቢ. ዶላር እንዲመልሱ ተጠይቀዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    - የቀድሞው መሪ ሳኒ አባቻ 4 ቢ. ዶላር ያህል መዝረፋቸው ተነግሯል

    የቀድሞው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ሳኒ አባቻ ዘርፈውታል የተባለውና የሙስና ምርመራ ለማድረግ በአሜሪካ የተያዘው ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንዲመለስ፣ የናይጀሪያ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መብቶች የተባለው የአገሪቱ የመብቶች ተከራካሪ ቡድን ለትራምፕ አስተዳደር ጥያቄ አቅርቧል፡፡ የቀድሞው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ሳኒ አባቻ፣ በስልጣን ዘመናቸው በድምሩ 4 ቢሊዮን ዶላር ያህል የህዝብ ሃብት መዝብረዋል መባላቸውን ያስታወሰው የሲኤንኤን ዘገባ፤ቡድኑም ከዚህ ገንዘብ ውስጥ በአሜሪካ እጅ ውስጥ ግማሽ ቢሊዮን ዶላር እንደሚገኝና ገንዘቡ ለህዝቡ እንዲመልስ ለትራምፕ አስተዳደር በደብዳቤ መጠየቁን አመልክቷል፡፡ ናይጀሪያ በኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ላይ ባለችበት በዚህ ወሳኝ ወቅት በአሜሪካ እጅ ላይ የሚገኘው የህዝብ ገንዘብ በአፋጣኝ መመለሱ አግባብ ነው፤ ትራምፕ ገንዘቡን ይመልሱና ህዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ስራዎች ላይ ይዋል ብሏል፤ ቡድኑ ባወጣው መግለጫ፡፡
የናይጀሪያው ፕሬዚደንት መሃመድ ቡሃሪ ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ መወያየታቸውንና ገንዘቡን ለመመለስ መስማማታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ በአንዳንድ ቢሮክራሲያዊ አሰራሮች ምክንያት ገንዘቡ ሳይመለስ የትራምፕ አስተዳደር ወደ ስልጣን መምጣቱን አስረድቷል፡፡እ.ኤ.አ በ1998 ከዚህ አለም በሞት የተለዩት የቀድሞው የናይጀሪያ ፕሬዚዳንት ሳኒ ኣባቻ፣ በተለያዩ አገራት የነበሯቸው ገንዘቦችና ንብረቶች እንዳይንቀሳቀሱ መታገዱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ስዊዘርላንድ 700 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ ለናይጀሪያ መንግስት መመለሷን ገልጧል፡፡

Read 1388 times
Administrator

Latest from Administrator