የደራሲ መክት ፋንቱ “ጳዝዮን” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ “ጳዝዮን” የሚለው ቃል፣ እንደ ወርቅና ዕንቁ የሚያንፀባርቅ የከበረ ማዕድን ማለት እንደሆነ በመግቢያው ላይ የተገለጸ ሲሆን መፅሐፉ እንደ ጳዝዮን የተከበሩ ሆነው ሳለ፣ በአዋቂ መጥፋትና ባለማስተዋል እንደ ትቢያ ስለተቆጠሩ መልካም አስተሳሰቦች፣ ራዕዮችና እሴቶች ይዳስሳል ተብሏል፡፡
በ264 ገጾች የተቀነበበው “ጳዝዮን”፤ ለአገር ውስጥ በ81 ብር ከ40 ሳንቲም፣ ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡