በደራሲ ኤል-ዳን ደርብ የተፃፈውና እውነተኛ ታሪክ ነው የተባለው “ታጋዮቹ በጎ-እ-ንደር የት ገቡ” የተሰኘ መፅሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
ደራሲው የሀገራችንን ያለፈ በጎና ጨለማ የሚባለውን ታሪክ ከራሱ ገጠመኝ ጋር እያጣቀሰ እንደሚያስቃኝ ተጠቁሟል፡፡
“ጠልተን የምንተወው አልያም ወደን የምንይዘው እውነት የለም፤ ወደድነውም ጠላነውም እውነት ያው እውነት ነው፤ እውነት ደግሞ የምርጫ ጉዳይ አይደለም” በሚል መርህ የተዘጋጀው መፅሐፉ፤ ለትውልድ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጥ ነው ተብሏል፡፡
በ41 ምዕራፎች ተከፋፍሎ፣ በ387 ገጾች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ200 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡