Sunday, 28 January 2018 00:00

በኦሮሚያ ክልል ከ2ሺ በላይ እስረኞች ተፈቱ

Written by 
Rate this item
(14 votes)


    የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ከአንድ ዓመት በፊት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰውን ብጥብጥ ተከትሎ፣ታስረው የነበሩ ከ2ሺ በላይ ዜጎችን መፍታቱን አስታወቀ፡፡ በትላንትናው ዕለት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳ በሰጡት መግለጫ፤2 ሺ 345 እስረኞች  በምህረት መፈታታቸውን የተናገሩ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 1 ሺ 568 ያህሉ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው እንደነበሩ  ገልጸዋል፡፡
መንግስት አገሪቱን ለማረጋጋትና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት፣ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱ መግለጹን ተከትሎ፣ ባሳለፍነው ሳምንት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ጨምሮ 500 የሚደርሱ እስረኞች የተፈቱ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል እርምጃም የዚሁ ውሳኔ አካል እንደሆነ ታውቋል፡፡

Read 8660 times