የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ከአንድ ዓመት በፊት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰውን ብጥብጥ ተከትሎ፣ታስረው የነበሩ ከ2ሺ በላይ ዜጎችን መፍታቱን አስታወቀ፡፡ በትላንትናው ዕለት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳ በሰጡት መግለጫ፤2 ሺ 345 እስረኞች በምህረት መፈታታቸውን የተናገሩ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 1 ሺ 568 ያህሉ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው እንደነበሩ ገልጸዋል፡፡
መንግስት አገሪቱን ለማረጋጋትና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት፣ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱ መግለጹን ተከትሎ፣ ባሳለፍነው ሳምንት ዶ/ር መረራ ጉዲናን ጨምሮ 500 የሚደርሱ እስረኞች የተፈቱ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል እርምጃም የዚሁ ውሳኔ አካል እንደሆነ ታውቋል፡፡
Published in
ዜና