ዲላይት ኤቨንትና ፕሮሞሽን ከዘቢዳር ቢራ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው “ፈታ አዲስ” የምግብና መጠጥ ፌስቲቫል፣ ዛሬና ነገ ቦሌ በሚገኘው ሞዛይክ ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ ክትፎ ቤቶች፣ የባህል ምግብ አዳራሾች፣ ጠጅ ቤቶችና ስጋ ቤቶች የሚሳተፉ ሲሆን ሰው እየበላና እየጠጣ በሀሴት አኩስቲክ ባንድ እንደሚዝናና አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡ የመግቢያ ዋጋው 150 ብር ነው ተብሏል፡፡
Saturday, 03 February 2018 13:05
“ፈታ አዲስ” የምግብና መጠጥ ፌስቲቫል ዛሬና ነገ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና