Print this page
Monday, 05 February 2018 00:00

“የጠፋው አዳም” የኪነ ጥበብ ምሽት ማክሰኞ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    የመጀመሪያው የአክሱም ስልጣኔ ባለቤቶች ሆነን ሳለ፣ ይህ ስልጣኔ መስፋት ሲገባው እንዴት ፈረሰ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት የሚደረግበት “የጠፋው አዳም” የኪነ ጥበብ ምሽት፣ የፊታችን ማክሰኞ ከቀኑ 11፡00 እስከ ምሽት 1፡45 በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡
በውይይቱ ላይ ከሚሳተፉት ምሁራን መካከል የዘርዓያዕቆብ ዘጠነኛ የልጅ ልጅ የሆኑት ሊቀ ጠበብትና ሳይንቲስት ገ/ማሪያም ማሞ፤ ስልጣኔያችን ለምን ፈረሰ፣ እንዴት ፈረሰ፣ ማንስ አፈረሰው? በሚለውና በምርምር በደረሱባቸው ሰባት ምልክቶች ዙሪያ ሰፊ ትንታኔ እንደሚሰጡ የሁነቱ አዘጋጅ አቶ ቤዛ ሁነኝ አብርሃም ተናግረዋል፡፡ ሊቀ ጠበብቱና ሳይንቲስቱ
ገ/ማሪያም ማሞ በበኩላቸው፤በአክሱም ስልጣኔ ላይ ባደረጓቸው ምርምሮችና ግኝቶች እንዲሁም ስልጣኔው እንዲቀጥል ምን መደረግ አለበት በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል፡፡ በዚህ ውይይት ለመታደም መግቢያው 70 ብር እንደሆነም ታውቋል፡፡ 

Read 2553 times
Administrator

Latest from Administrator