Print this page
Sunday, 04 February 2018 00:00

በሳኡዲ ለ140 ክፍት የስራ ቦታ፣ 107,000 ሴቶች አመልክተዋል

Written by 
Rate this item
(6 votes)

የሳኡዲ አረቢያ መንግስት የፓስፖርት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ በ140 የተለያዩ ክፍት የስራ ቦታዎች ላይ ሴቶችን ቀጥሮ ለማሰራት ባወጣው ማስታወቂያ፤ ከ107,000 በላይ አመልካቾች መቅረባቸውን ኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
በአውሮፕላን ማረፊያዎችና በድንበር አካባቢ መስሪያ ቤቶች መስራት ለሚፈልጉ ስራ ፈላጊዎች የወጣው የክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ፤ በድረ ገጽ አማካይነት በተሰራጨ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ107,000 በላይ አመልካቾች መቅረባቸው ያስደነገጠውና መስተንግዶው ከአቅሙ በላይ የሆነበት ዳይሬክቶሬቱ፤ በአፋጣኝ ማስታወቂያውን ማንሳቱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያው ቢያንስ ሁለተኛ ደረጃን ያጠናቀቁና ከ25 እስከ 35 አመት በሚገኘው የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ አመልካቾችን ብቻ መጋበዙን የጠቆመው ዘገባው፤ በሳኡዲ አረቢያ የሴቶች ስራ አጥነት 33 በመቶ ላይ እንደሚገኝም አስታውሷል፡፡

Read 5969 times
Administrator

Latest from Administrator