Print this page
Sunday, 11 February 2018 00:00

“ንጉስ ዘርዓ ያዕቆብና ሌሎች ግለ ወጎች” እና “የህሊና መንገድና ሌሎች ልቦለዶች” ሰኞ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በአንዱአለም አባተ (የአፀደ ልጅ) የተሰናዱት “ንጉስ ዘርዓ ያዕቆብና ሌሎች ግለ - ወጎች” እና “የህሊና መንገድና ሌሎች ልቦለዶች” የተሰኙ መፅሀፎች ሰኞ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል እንደሚመረቁ የምርቃቱ አዘጋጅ መገዘዝ መልቲ ሚዲያና ቴአትር ፕሮሞሽን አስታወቀ፡፡ በዕለቱ የፍልስፍና ምሁሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ “ንጉስ ዘርዓ ያዕቆብና ሌሎች በተሰኘው መፅሀፍ ላይ ልዩ ዳሰሳ የሚያቀርቡ ሲሆን ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ጀዋሬ ደግሞ መፅሀፉ ለቴአትር ትምህርትና ለደራሲያን ያለውን ፋይዳ ለታዳሚው ያካፍላሉ ተብሏል፡፡ በአ.አ.ዩ የጋዜጠንነትና ተግባቦት መምህር የሆኑት ዶ/ር ተሻገር ሽፈራው ደግሞ “የህሊና መንገድ እና ሌሎችም” በተሰነው መፅሀፍ ላይ ዳሰሳ እንደሚያቀርቡም ታውቋል፡፡ “ንጉስ ዘርዓ ያዕቆብ” የተሰኘው መፅሐፍ ደራሲው በመረጣቸው ተሪካዊያን ግለሰቦች ላይ በመመርኮዝና በተውኔታዊ አቀራረብ ያሰናዳቸው ታሪኮች የተካተቱበት ሲሆን ቁልፍ ርዕሰ ጉዳዮችም በፍትህ፣ በእውነት፣ በበቀል፣ በክህደትና በቃል ኪዳን ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ ታሪኮቹ ምናባዊ ልብ ወለድ ቢሆኑም ከታሪክና ከቅዱሳት ድርሳናት ዋናውን የትረካ ጭብጥ ይዘው በመነሳታቸው በስነ - ፅሁፍ ዓለም “ንቡር ጠቃሽ” ከሚባለው የስነ ፅሁፍ ዘውግ ይመደባልም ተብሏል፡፡ በ124 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ60 ብርና በ15 ዶላር እየተሸጠ ነው፡፡ ደራሲው “የህሊና መንገድ እና ሌሎም አጫጭር ልቦለዶች” የተሰኘ አዲስ መፅሐፍም ለንባብ አብቅቷል፡፡ በዚህ መፅሀፍ ውስጥ በተለያየ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ 13 ያህል አጫጭር ልቦለዶች ተካተውበታል፡፡ በ118 ገፆች የተመጠነው መፅሐፉ በ50 ብርና በ10 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 5654 times Last modified on Saturday, 10 February 2018 12:01
Administrator

Latest from Administrator