Sunday, 11 February 2018 00:00

79ኛው ግጥም በጃዝ የፊታችን ረቡዕ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(4 votes)

 የአድዋ በዓል ላይ ልዩ ዝግጅቱን ያደረገው 79ኛው “ግጥም በጃዝ” የኪነ ጥበብ ምሽት፣ የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በምሽቱ ፕሮግራም ዶ/ር ዓለማየሁ አረዳ ዲስኩር የሚያቀርቡ ሲሆን ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ገጣሚና ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን፣ ዶ/ር ይርጋ ገላው፣ አርቲስት አለማየሁ ታደሰ፣ ምንተስኖት ማሞ፣ ይታገሱ ጌትነትና ሚካኤል ሚሊዮን ስራቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ደራሲነት የተሰናዳ አጭር ተውኔት በአርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ እንደሚተወን ታውቋል፡፡

Read 4619 times