Print this page
Saturday, 10 February 2018 12:01

ከ6 ሺ በላይ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚሳተፉበት የሂሳብ ጥያቄና መልስ ውድድር ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 ከ5 ሺ ብር እስከ 10 ሺ ብር ሽልማት ተዘጋጅቷል
 
    ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ እውቅናን በማግኘት በቃላዊ ሂሳብ ስሌት፣ በሶሮባንና በሁለንተናዊ የአዕምሮ ዕድገት ላይ ልዩ ልዩ ስልጠናዎችንና የሂሳብ ስሌት ውድድሮችን ሲያካሂድ የነበረው “ማይንድ ፕላስ ማትስ” ተቋም ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ የሂሳብ ትምህርት ጥያቄና መልስ ውድድር ያካሂዳል፡፡
ውድድሩ በአራተኛ፣ በስድስተኛ፣ በስምንተኛ፣ በ10ኛና በ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል የሚካሄድ ሲሆን ከአማራ የባህር ዳር፣ ከኦሮሚያ የአሰላና አዳማ፣ ከትግራይ የመቐለ፣ እንዲሁም የአዲስ አበባና የድሬደዋ ከተማ ተማሪዎች እንደሚሳተፉና በመጀመሪያው ዙር 10ሺህ ያህል ተማሪዎች ለውድድር ቀርበው እንደነበር “ማይንድ ፕላስ ማትስ” ገልጿል፡፡ እስካሁንም ከአዲስ አበባ 3126፣ ከመቀሌ 1569፣ ከባህር ዳር 659፣ ከአሰላ 300፣ ከአዳማ 300 ከድሬደዋ 450 በድምሩ 6404 ተማሪዎች ክልላቸውን ወክለው የሚቀርቡ ሲሆን በየክፍል ደረጃቸው 15 ተማሪዎች ለመጨረሻው ዙር ቀርበው፣ የአሸናፊዎች አሸናፊ የመለየት ስራ እንደሚሰራም ተቋሙ ገልጿል፡፡
የፈተናዎቹ ጥያቄዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና በኮተቤ ሜትሮ ፖሊታንት ዩኒቨርሰቲ መምህራን በጥንቃቄ የተዘጋጁ መሆናቸውንም ተቋሙ ጨምሮ ገልጿል፡፡ በውድድሩ 1ኛ ለሚወጣ 10 ሺህ ብር፣ 2ኛ ለሚወጣ 7 ሺህ ብር፣ በ3ኛነት ለሚያሸንፍ የ5 ሺህ ብር ሽልማት መዘጋጀቱን የገለፀው “ማይንድ ፕላስ ማትስ”፤ የመጨረሻውና የሽልማቱ ሥነ ስርዓት በእለተ ፋሲካ በተመረጠ የቴሌቪዥን ጣቢያ በቀጥታ እንደሚተላለፍ አስታውቆ፣ ውድድሩ መካሄዱም ሆነ በቴሌቪዥን ቀጥታ መተላለፉ ሌሎች ተከታይ ተማሪዎችን በማነቃቃት፣ በሂሳብ ትምህርት ላይ ፍላጎት እንዲያድርባቸውና ለውድድር ዝግጁ እንዲሆኑ ያደርጋልም ተብሏል፡፡

Read 4703 times
Administrator

Latest from Administrator