Print this page
Sunday, 18 February 2018 00:00

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከትላንት ጀምሮ ታውጇል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 119 እስረኞች ክሳቸው ተቋረጠ ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ፣ ብርጋዴል ጀነራል ተፈራ ማሞና ብርጋዴል ጀነራል አሳምነው ፅጌ ይገኙበታል

     የሚኒስትሮች ም/ቤት ከትላንትናው እለት ጀምሮ የሚፀና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀ ሲሆን ለ6 ወራት እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀው በህዝባዊ አመፅና አድማ፣ የመንግሥትና የግል ንብረቶች ውድመትና የሰው ህይወት መጥፋትን ለማስቀረት ነው ተብሏል፡፡ አዋጁ ከ15 ቀናት በኋላ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ቀርቦ እንደሚፀድቅ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል 119 እስረኞች በትላንትናው እለት ክሳቸው የተቋረጠ ሲሆን 56 የግንቦት 7 አባላት ተብለው የተጠረጠሩ እንዲሁም 41 የኦነግ አባላት ተብለው የተጠረጠሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡
ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተደረጉት መካከል ኮ/ል ደመቀ ዘውዱ፣ ብርጋዴል ጀነራል ተፈራ ማሞና ብርጋዴል ጀነራል አሳምነው ፅጌ ይገኙበታል፡፡

Read 4889 times
Administrator

Latest from Administrator