በጀርመኑ የቴክኒክ ተራድኦ ድርጅት (ጂአይዜድ) እና ሲኤንኤፍኤ በተሰኙ ዓለም አቀፍ ተቋማት እገዛ በአርሲ ዞን ሁሩታና ሳጉሬ ወረዳዎች፣ከ60 ሺ ዩሮ በላይ በሆነ ወጪ፣ ዘመናዊ የግብርና ግብአቶች ማስፋፊያ ማዕከላት ተገነቡ፡፡
ሰሞኑን የተመረቁት እነዚህ የግብርና ማዕከላት፣ ዘመናዊና ጥራት ያላቸው የሰብል ዘሮችን፣ የአረም መከላከያ መድሐኒቶችና የእንስሳት ህክምና ምርቶችን በሰለጠኑ ሠራተኞችና በተመጣጣኝ ዋጋ፣ ለአርሶ አደሮች ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
ማዕከላቱን የተራድኦ ድርጅቶችና የአካባቢው ሥራ ፈጣሪ ወጣቶች በእኩል መዋጮ ያስገነቧቸው ሲሆን ከአገልግሎት ሽያጭ የሚሰበሰበው ገቢም ለወጣቶቹ እንደሚሆን ተነግሯል፡፡ አንድ ማዕከል ለ25 ሺህ ያህል አርሶ አደሮች እንደሚያገለግል የተጠቆመ ሲሆን ማዕከላቱ ግብአቶችን ከማቅረብ ጐን ለጐን፣ለአርሶ አደሮች የምክርና ስልጠና አገልግሎት እንደሚሰጡ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጧል፡፡
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ