Saturday, 17 February 2018 15:03

በአፍጋኒስታን አምና ብቻ 10 ሺ ንጹሃን ዜጎች ላይ ግድያና ጥቃት ተፈጽሟል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በአፍጋኒስታን ባለፈው የፈረንጆች አመት 2017 በተካሄዱ ብጥብጦች፣ ከ10 ሺህ በላይ በሚሆኑ የአገሪቱ ንጹሃን ዜጎች ላይ የግድያ ወይም የመቁሰል አደጋ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በአፍጋኒስታን በአመቱ 3 ሺህ 438 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን የጠቆመው ተመድ፤7 ሺህ 15 ያህል የሚሆኑትም ለመቁሰል አደጋ መዳረጋቸውን ያመለከተ ሲሆን በዜጎች ላይ ከተፈጸሙት ግድያዎች ወይም የማቁሰል ድርጊቶች መካከል ከስድሳ በመቶ በላይ የሚሆኑት የተፈጸሙት በጸረ-መንግስት ሃይሎች በተደረጉ የቦንብ ጥቃቶች መሆኑንም አመልክቷል፡፡ በአመቱ በአፍጋኒስታን ንጹሃን ዜጎች ላይ ከተፈጸሙት ጥቃቶች መካከል ታሊባን 42 በመቶ፣ አይሲስ 10 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸው ያስታወሰው መግለጫው፤ በአሜሪካ የአየር ድብደባዎች ለሞትና ለመቁሰል አደጋ የሚጋለጡ ዜጎች ቁጥርም እያደገ ነው ብሏል፡፡
በ2017 የፈረንጆች አመት አፍጋኒስታናውያን ህጻናትና ሴቶች በከፍተኛ ሁኔታ የጥቃት ሰለባ መሆናቸውን የጠቆመው መግለጫው፤በአመቱ 359 ሴቶች መገደላቸውንና 865 ሴቶች ደግሞ መቁሰላቸውን፤ 861 ህጻናት መገደላቸውንና 2 ሺህ 318 መቁሰላቸውን አስታውቋል፡፡

Read 1281 times