በኢትዮጵያ የተፈጠረው አለመረጋጋትና የሠላም እጦት እንዳሳሰበው የጠቆመው የአፍሪካ ህብረት፤ ሁሉም ኢትዮጵያውያንና መንግስት ለሠላምና መረጋጋት ቅድሚያ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር ሙሣ መሃመት ፋኪ ከትናንት በስቲያ ለመገናኛ ብዙሃን ባሠራጩት መግለጫ፤ ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተዋንያን ሠላምና መረጋጋትን ከሚነሣ ድርጊት መታቀብ አለባቸው ብለዋል፡፡
“መንግስትና የሃገሪቱ ህዝብ ችግሩን በመግባባት እንደሚፈቱት እምነት አለኝ” ያሉት ሊቀ መንበሩ፤ መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ቃል መግባቱንም ህብረቱ በአዎንታ እንደሚቀበለው አስታውቀዋል፡፡
“የኢትዮጵያ መረጋጋት ለህዝቧ፣ ለቀጠናውና ለመላው አፍሪካ በእጀጉ አስፈላጊ ነው” ያሉት ሙሣ ፋኪ፤ መንግስትና ሁሉም የሃገሪቱ ባለድርሻዎች በሃላፊነት ስሜት እንዲንቀሣቀሱ አሳስበዋል፡፡
Published in
ዜና