በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይካትሪ ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር በሆኑት ዶ/ር ዮናስ ባህረጥበብ የተፃፈውና በኦቲዝምና ችግሮቹ ላይ አተኩሮ የተሰናዳው “አይኔን ተመልከተኝ” የተሰኘው መፅሐፍ፣ ዛሬ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴዝ ይመረቃል፡፡
በምርቃት ስነ - ስርዓቱ ላይ የህክምና ባለሙያዎች፣ የኦቲዝም ተጠቂ ህፃናትና ቤተሰቦቻቸው፣ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ሌሎች እንግዶች የሚገኙ ሲሆን በችግሩ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንግግሮች፣ ውይይቶችና የኪነ - ጥበብ ስራዎች ለታዳሚው እንደሚቀርቡም የምርቃቱ አዘጋጅ ይሳቃል ኢንተርቴይንመንት በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡