Saturday, 03 March 2018 11:17

ሰሜን ኮርያ ለሶርያ የኬሚካል ጦር መሳሪያ፤ ጥሬ ዕቃዎች ሸጣለች ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ሰሜን ኮርያ ባለፈው ሳምንት ብቻ ከ400 በላይ ዜጎቿ በክሎሪን ጋዝ ጥቃት ለሞት ለተዳረጉባትና በእርስበርስ ጦርነት አሰቃቂ ውድመት እያስተናገደች ለምትገኘው ሶርያ፤ ባለፉት አምስት ዓመታት 40 ጊዜያት ያህል፣ ለኬሚካል ጦር መሳሪያዎች ምርት በጥሬ እቃነት የሚውሉ ቁሳቁሶችን መሸጧን ተመድ አስታውቋል፡፡
ሰሜን ኮርያ እ.ኤ.አ ከ2012 እስከ 2017 በነበሩት ዓመታት፣ አለማቀፍ ማዕቀቦችን በመጣስ፣ ለኬሚካል ጦር መሳሪያዎች ምርት የሚውሉ ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ሶርያ መላኳንና የአገሪቱ የሚሳኤል ባለሙያዎችም፣ በሶርያ የጦር መሳሪያ ማምረቻ ማዕከላት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የሚያረጋግጥ መረጃ ማግኘቱን፣ተመድ ባወጣው መረጃ ማስታወቁን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ሶርያ ከሰሜን ኮርያ ለገዛቻቸው ለእነዚህ ጥሬ ዕቃዎች፣ “ሳይንቲፊክ ስተዲስ ኤንድ ሪሰርች ሴንተር” የተባለው የሶርያ መንግስት ተቋም፣ በሌሎች ኩባንያዎች ስም ክፍያ መፈጸሙን አረጋግጫለሁ ያለው ተመድ፤ተቋሙ የተመሰረተው ለምርምር ቢሆንም በሶስት ማዕከላት ውስጥ የኬሚካል ጦር መሳሪያዎችን ሲያመርት እንደነበር መረጋገጡንም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 2324 times