የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማህበርና የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተባብረውበት ባለፈው ሰኞ “ሥነጽሑፍና ሴቶች” ሥልጠና ነገ እንደሚጠናቀቅ ማህበሩ አስታወቀ፡፡ የማህበሩ የባህርዳር ቅርንጫፍ ባዘጋጀው ሥልጠና ሂደት በቅርቡ በአዲስ አበባ የተመረቀው የዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ “እውነት ማለት የኔ ልጅ” እና የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማህበር “እኛ” ቁጥር 4 የግጥም መፃሕፍት ትናንት ሥልጠናው በተዘጋጀበት ባህር ዳር ተመርቀዋል፡፡