“ድርና ማግ” የኪነ - ጥበብ ምሽት ለ3ኛ ጊዜ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ መገናኛ በሚገኘው አፋራንሲስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ይካሄዳል። በተለይ የአሁኑን ምሽት ለየት የሚያደርገው የሚቀርቡት ዝግጅቶች 122ኛውን የአድዋ ድል በዓል የሚዘክሩ በመሆናቸው ነው ተብሏል፡፡
በዝግጅቱም ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ገጣሚና ተዋናይ ተፈሪ አለሙ፣ ሰዓሊና ገጣሚ አገኘሁ አዳነ፣ የሙዚቃ ባለሙያና ተመራማሪ ሰርፀ ፍሬ ስብሃት፣ እንዲሁም ገጣሚዎቹ ረድኤት ተረፈ፣ ዳንኤል ስዩምና ደሳለኝ ብርሃኑ ስራዎቻቸውን ለታዳሚው እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ መሶብ ባህላዊ ባንድ በአዳዲስ ሙዚቃዎቻቸው ዝግጅቱን አድምቀው እንደሚያመሹም የፕሮግራሙ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ አስታውቋል፡፡
Sunday, 04 March 2018 00:00
3ኛው ድርና ማግ የኪነ ጥበብ ምሽት ሐሙስ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና