Tuesday, 13 March 2018 12:59

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማሟያ 375 ሚ. ዶላር አበደረ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ እስከ 2025 ለማሳካት ለያዘችው ሁሉንም ዜጋ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ እቅድ የሚውል የ375 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከዓለም ባንክ ማግኘቷ ታውቋል፡፡
ከዓለም ባንክ ሰሞኑን የተገኘው የገንዘብ ብድር በተለይ በቀጣዮቹ 5 ዓመታት ውስጥ ለአንድ ሚሊዮን የገጠር ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ለተያዘው እቅድ አጋዥ ይሆናል ተብሏል። በአጠቃላይ የ5 ዓመቱ ፕሮጀክት 1.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚጠይቅም ታውቋል፡፡
ኢትዮጵያ ከፍተኛ የታዳሽ ኃይል የማምረት አቅም እንዳላት በመግለጫው የተጠቆመ ሲሆን ፕሮጀክቱም በቁርጠኝነት ከተሰራ ስኬታማ ይሆናል ተብሏል፡፡
ሀገሪቱ ካላት ሃይድሮ ኤሌክትሪክ አቅም ባሻገር ከፀሐይ፣ ከንፋስና ከጂኦተርሚናል ኃይል የማመንጨት ከፍተኛ አቅም እንዳላት የዓለም ባንክ ሪፖርት ጠቁሟል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ባለፉት 10 ዓመታት ውጤታማ የኤሌክትሪክ ማዳረስ ፕሮግራም ዘርግቶ በሀገሪቱ የሚገኙ ከተሞችንና መንደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑም ተመልክቷል- በመግለጫው፡፡

Read 5109 times