Print this page
Tuesday, 13 March 2018 12:59

የዩኒቨርሲቲ መምህሩና ጦማሪው ስዩም ተሾመ ታሰሩ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አስተያየት በመስጠትና የሰሉ ሂሳዊ ጽሁፎችን በማቅረብ የሚታወቁት የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ወሊሶ ካምፓስ መምህር የሆኑት አቶ ስዩም ተሾመ ሰሞኑን መታሰራቸው ታውቋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ መምህሩና ጦማሪው አቶ ስዩም ተሾመ የመታሰራቸው ጉዳይ ከትናንት በስቲያ በማህበራዊ ሚዲያዎች የተነገረ ሲሆን ስለ ሁኔታው ለማወቅ ወደ ቅርብ ወዳጃቸው በመደወል መታሰራቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
የፖለቲካ ተንታኙ አቶ ስዩም ተሾመ፤ ሐሙስ ጠዋት 4 ሰዓት ገደማ ወሊሶ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በፀጥታ ኃይሎች መወሰዳቸው የታወቀ ሲሆን ምንጮች በኮማንድ ፖስቱ ሳይታሰሩ እንዳልቀረ ቢገምቱም ለማረጋገጥ ግን አልተቻለም፡፡
በመንግስት ላይ ጠንካራ ትችቶችን በድፍረት በመሰንዘር የሚታወቁት የዩኒቨርሲቲ መምህሩ አቶ ስዩም ተሾመ፤በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ከአገሪቱ የፖለቲካ ቀውስ ጋር በተያያዘ ትንተናዎችና የመፍትሄ ሃሳቦች በመስጠት ትኩረት ስበው ቆይተዋል፡፡

Read 6997 times
Administrator

Latest from Administrator