ከአመታት በፊት በአለማችን የስማርት ፎን ገበያ ከቀዳሚዎች ተርታ ይሰለፍ የነበረው የአሜሪካው ኩባንያ ብላክቤሪ፣ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎቼን የቅጂ መብት በመጣስ ተጠቅሞብኛል ሲል በታዋቂው የማህበራዊ ድረገጽ ኩባንያ በፌስቡክ ላይ ክስ መመስረቱ ተነግሯል፡፡
ፌስቡክ ፈጠራዎቼን በመስረቅ በዋትሳፕና በኢንስታግራም አፕሊኬሽኖቹ ላይ ተጠቅሞብኛል ሲል ክስ የመሰረተው ብላክቤሪ፤ከአመታት በፊት አብረን ልንሰራ ተስማምተን ነበር፣ ውሉን አፍርሶ ፈጠራዎቼን ተጠቅሞብኛል ብሏል- ቢቢሲ እንደ ዘገበው፡፡
ብላክቤሪ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሽያጩ እየቀነሰና ተወዳዳሪነቱና ተወዳጅነቱ እየቀነሰ መምጣቱን ተከትሎ፣ ከ2 አመታት በፊት ስማርት ፎን ማምረት ማቆሙን የጠቆመው ዘገባው፤ባለፈው አመትም በኖክያ ላይ ተመሳሳይ የቅጂ መብት ጥሰት ክስ መስርቶ እንደነበር አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ