Print this page
Tuesday, 13 March 2018 13:37

የጀርመን የባህል ማዕከል ዘመናዊ ቤተ-መፃህፍት አስመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የጀርመን የባህል ማዕከል (ጎተ) አዲስና ደረጃውን የጠበቀ ቤተ መፃህፍት ከትላንት በስቲያ ምሽት ላይ አስረመቀ፡፡ ቤተ መፅሐፍቱ ሶስት የተለያዩ ክፍሎችን የያዘ ሲሆን አንደኛው መፅሐፍትን ለማንበብና በጥሞና ሀሳቦችን ለማውጠንጠን የተዘጋጀ ሲሆን ከ20 ሰዎች በላይ በአንድ ጊዜ ማስተናገድ ይችላል ተብሏል፡፡
2ኛው ክፍል ሲዲ፣ ኦዲዮ መፅሐፍት፣ ፊልም ማየት ለሚፈልጉና ኢንተርኔት መጠቀም ለሚፈልጉ ተጠቃሚዎች የተሰናዳ ክፍል ሲሆን አምስት አይፖዶችና ላፕቶፖችም የሚገኙበት እንደሆነና በአንዴ 18 ያህል ሰዎች የማስተናገድ አቅም ያለው ስለመሆኑ የቤተ - መፅሐፍትና የኢንፎርሜሽን ኃላፊው አቶ ዮናስ ታረቀኝ ተናግረዋል፡፡ ሶስተኛው ክፍል ደግሞ አነስተኛ ስቱዲዮና አረንጓዴ ስክሪን የተገጠመለት ክፍል ሲሆን ይህ ክፍል ስለፊልም በቡድን ለሚወያዩ፣ ፊልም ኤዲት ለሚያደርጉ፣ ስቱዲዮ ውስጥ ኢንተርቪው ለሚቀርፁና ለመሰል ተግባራት የሚያገለግል እንደሆነ የገለፁት አቶ ዮናስ በአጠቃላይ ቤተ - መፅሐፍቱ “መልቲ ፊንክሽናልና መልቲ ሚዲያ” ሆኖ ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡
በፊት የነበረውን የተለመደውን ቤተ - መፅሀፍት ለመቀየር ጥናት መስራቱንና ከውጭ የመጣች ባለሙያ የተለያዩ ተጠቃሚዎች የቋንቋ ተማሪችንና ሌሎችንም ከጎተ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ተጠቃሚዎችን፣ ቃለ መጠይቅ ካደረገችና ፍላጎታቸው ከታወቀ በኋላ የቤተ መፅሐፍቱ ዲዛይን መስራቱን የገለፁት ኃላፊው ግንባታው አራት ወር እንደፈጀና ከ200 ሺህ ዩሮ በላይ እንደወጣበት ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በምርቃት ስነ - ስርዓቱ ላይ ከንባብ ጋር የሚሰሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባህል ማዕከሉ ኃላፊች ታድመው ነበር፡፡

Read 1383 times
Administrator

Latest from Administrator