Tuesday, 13 March 2018 13:38

ማልታ ጊነስ “ለማልታ ቬተር” ውድድር 10 ኢትዮጵያውያንን ያሳትፋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በናይጄሪያ 1ኛ የሚወጣ አሸናፊ ግማሽ ሚሊዮን ብር ይሸለማል

በዲያጂዮ ስር የሚመረተው ማልታ ጊነስ፤ “ማልታ ቬተር” በተባለና በአራት የአፍሪካ አገራት መካከል ለሚደረግ የተለያዩ አዝናኝና ስፖርታዊ ውድድሮች ለመጨረሻ ዙር ያለፉ 10 ኢትዮጵያውያን ወጣቶችን ወደ ናይጄሪያ ሊልክ ነው፡፡ በናይጄሪያ ሌጎስ በሚደረገው በዚህ ውድድር አንደኛ የሚወጣ አሸናፊ 20 ሺህ ዶላር (ግማሽ ሚሊዮን ብር) እንደሚሸለም የማልታ ጊነስ ብራንድ ማናጀር ወ/ሪት ረድኤት ዘገየ ባለፈው ሰኞ በጎልደን ቱሊፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡
በዚህ ውድድር የጋና የአይቬሪኮስት፣ የናይጄሪያና የኢትዮጵያ ወጣቶች የሚሳተፉ ሲሆን ውድድሩ ብዙ ክህሎቶችን የማይጠይቅና ቀላል በሚመስሉ ጨዋታዎችና ስፖርታዊ ውድድሮች የተሻለና ፈጣን ፈጠራን በመጠቀም የአስተሳሰብ አድማስን የሚያሰፋ እንደሆነም ተገልጿል፡፡
ውድድሩ ከህዳር 2010 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በተከታታይ ሲካሄድ መቆየቱንና በየዙሩ እያሸነፉ ለመጨረሻው ዙር ያለፉት ስድስት ወንዶችና አራት ሴት ወጣቶች ከየካቲት 30 ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት በናይጄሪያ ሌጎስ በሚደረግ ውድድር የሚሳተፉ ሲሆን አሸናፊው ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደሚሸለም ኃላፊዎቹ ተናግረዋል፡፡

Read 3606 times