80ኛው ዙር “ግጥም በጃዝ” የኪነ - ጥበብ ምሽት የፊታችን ረቡዕ መጋቢት 5 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ ገጣሚና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ፣ የትነበርሽ ንጉሴ፣ ሎሬት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ትዕግስት ማሞና ምስራቅ ተረፈ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን በዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ የተደረሰ አጭር ተውኔት በአርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ ለታዳሚ እንደሚቀርብም ታውቋል፡፡