Print this page
Tuesday, 20 March 2018 11:22

“Drink with the Devil” ወደ አማርኛ ተተረጎመ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የዝነኛው ደራሲ ጃክ ሂግኒስ ተዋቂ መፅሐፍ የሆነው “ድሪንክ ዊዝ ዘ ዴቭል” በተርጓሚ መልዓከ ተሰማ “ሰዎቹ” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተመልሶ ለንበብ በቃ፡፡
የጃክ ሂግኒስ ሌሎች ሥራዎች በሚሊዮን ቅጂዎች እንደተቸበቸቡለትና አብዛኛዎቹ መፅሐቱ በ38 ቋንቋዎች ተተርጉመው በመላው ዓለም መሰራጨታቸውን፣ ብዙዎቹም ወደ ፊልምነት መቀየራቸውን ተርጓሚው ጠቁሟል፡፡ “ሰዎቹ” በሚል ወደ አማርኛ የተተረጎመውም መፅሐፍ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በአፅንኦት ያወደሱትና ያደነቁት ነው ብሏል - ተርጓሚው፡፡
“ሰዎቹ ለፖለቲካ ድርጅታቸው ህልውና በሚል ሽፋን የግል ቢዝነሳቸውን ለማስፋትና ሚሊየነር ለመሆን በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር የወርቅ ነዶ ዘርፈዋል፡፡  በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ የሰው ደም እንደ ዋዛ ተገብሯል… ዓለማችንም መቼ እና እንዴት እነኚህን የፖለቲካ ቧልተኛና ዳንኪረኛ “ነፃ አውጪዎችን” ነፃ አውጥታ ወደ ትከክለኛው የፍትህና እውነት ትራክ ላይ አሳፍራ መጓዝ እንዳለባት ግራ የተጋባች መስላለች” … ይላል መፅሐፉ ጀርባ ላይ የሰፈረው ቅንጭብ ታሪክ። በ216 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ61 ብር ለሽያጭ ቀርቧል፡፡

Read 5584 times
Administrator

Latest from Administrator