Print this page
Saturday, 14 April 2018 14:45

ቢል ጌትስና አንጀሊና ጆሊ ከፍተኛ አድናቆትን በማትረፍ ቀዳሚ ሆነዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)


    በአለማችን በተለያዩ መስኮች እጅግ ከፍተኛ ተወዳጅነትና ተደናቂነትን ያተረፉ ግለሰቦችን ዝርዝር በየአመቱ ይፋ የሚያደርገው ዩጎቭ፣ ከሰሞኑም የ2018 ምርጦችን ይፋ ያደረገ ሲሆን የማይክሮሶፍቱ መስራች አሜሪካዊው ቢሊየነር ቢል ጌትስና ታዋቂዋ የሆሊውድ ተዋናይት አንጀሊና ጆሊ ቀዳሚነቱን ይዘዋል፡፡
ቢል ጌትስና አንጀሊና ጆሊ ላለፉት ሶስት ተከታታይ አመታት የአለማችን ቀዳሚዎቹ እጅግ ተወዳጅ ዝነኞች ሆነው መዝለቃቸውን የዘገበው ዘ ኢንዲፔንደንት፤ በዘንድሮው ዝርዝር ውስጥ በሁለቱም ጾታዎች 20 ሰዎች መካተታቸውንም አመልክቷል፡፡
ዩጎቭ ከ37 ሺህ በላይ ከሚሆኑ የ35 የአለማችን አገራት ዜጎች በድረገጽ በሰበሰበው የድምጽ አሰጣጥ መሰረት፤ በወንዶች ዘርፍ ከቢል ጌትስ ቀጥለው የአለማችን የአመቱ ተደናቂ የሆኑት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ መሆናቸውንና ቻይናዊው የፊልም አክተር ጃኪ ቻን ሶስተኛ ደረጃን መያዙንም ጠቁሟል፡፡
የቢዝነስ ሰዎችና የስፖርቱ አለም ከዋክብት በበዙበት በዘንድሮው ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት መካከል ዋረን በፌ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ሜሲና ዴቪድ ቤካም ይገኙበታል ያለው ዘገባው፤በፖለቲካው መስክ ከተመረጡት መካከልም የቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂፒንግ፣ ዶናልድ ትራምፕ እና ቭላድሚር ፑቲን እንደሚገኙበት አስታውቋል፡፡
የመዝናኛው መስክ ዝነኞች በብዛት በተካተቱበት በሴቶች ዘርፍ በአንጻሩ፣ የሁለተኛነትን ደረጃ የያዙት የቀድሞዋ የአሜሪካ ቀዳማዊት እመቤት ሚሼል ኦባማ ሲሆኑ ታዋቂዋ የቶክሾው አቅራቢ ኦፕራ ዊንፍሬይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
እስከ አስረኛ ባለው ደረጃ ውስጥ ከተካተቱት የአለማችን ሴቶች ውስጥ ቴለር ስዊፍት፣ ማዶና፣ ሂላሪ ክሊንተንና የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ መርኬል እንደሚገኙበትም ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Read 1543 times
Administrator

Latest from Administrator