Print this page
Monday, 07 May 2018 09:35

‹‹…ኤችአይቪ ቫይረስ..…ያልታቀደ እርግዝና…››

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    ኤችአይቪ ቫይረስ በሚያስከትለው የአቅም መዳከም የተነሳ በመውለድ እድሜ ላይ ያሉ ሴቶችን ጤንነት የሚፈታተንና እንዲሁም ቫይረሱ ወደ ቤተሰብ የመተላለፍ እድሉን ስለሚጨምር ወደ ፊት ልጅ ለመውለድ የሚኖራትን ፍላጎት ሊፈታተነው ይችላል፡፡ ስለዚህም ያልተፈለገ እርግዝና መከላከያ መጠቀም ያልተፈለገ እርግዝናን ከመከላከሉም ባሻገር ቫይረሱ ከእናት ወደልጅ የሚኖ ረውን መተላለፍ ይቀንሳል፡፡
ከላይ የተጠቀሰው እውነታ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ንጹህ አዲስና ዶ/ር እስክንድር ከበደ ካደረጉት ጥናት የተወሰደ ነው፡፡ ጥናቱ የተደረገው በአዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ፤ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል እና ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል በእርግዝና ወቅት ክትትል ከሚደረግበት ክሊኒክ ነው፡፡ በሶስቱ ሆስፒታሎች በአመት እስከ 12.000/አስራ ሁለት ሺህ እናቶች የሚወልዱ ሲሆን ጥናቱ የተደረገውም April-August/2016/ ድረስ ነው፡፡
የኤችአይቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ያለ ሴቶች እርግዝናን በእቅድ ወይንም በፕላን እንዲያ ደርጉ የሚመክረውን ጥናት ለማድረግ በጥናቱ የተካተቱ ሴቶች በሙሉ ቫይረሱ ያለባቸው ሲሆኑ በተጠቀሱት ሆስፒታሎች የእርግዝና ክትትል በማድረግ ላይ የነበሩ ናቸው፡፡ በእርግጥ ቫይረሱ በደማቸው ቢኖርም በምጥ ላይ የነበሩ ወይንም ጽንስ በማቋረጥ ላይ የነበሩ እና የተረ ገዘው ልጅ ሞት የገጠማቸውን እናቶች ጥናቱ አላካተተም፡፡ በጥናቱ የተካተቱት እናቶች 183/ሲሆኑ በተለይም 173/እናቶች 94% የሚሆኑት ለጥናቱ ጠቃሚ መረጃን በመስጠት ተሳትፈዋል፡፡   
ሰውነት ሕመምን እንዲቋቋም የሚያስችለውን አቅም የሚፈታተነው ኤችአይቪ ቫይረስ ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት ከፍተኛውን የስርጭት ቁጥር የያዘ ሲሆን ከዚህም ሴቶች 58% የሚሆነውን በቫይረሱ የመያዝ ድርሻ ይይዛሉ፡፡ የኤችአይቪ ስርጭት በህጻናቱም በኩል ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት ከፍ ያለ ቁጥር የተመዘገበበት ሲሆን በአለም በአመት በአዲስ በቫ ይረሱ ከሚያዙት 98% የሚሆኑት በዚሁ ክልል የሚኖሩ ናቸው፡፡
እርግዝናን በእቅድ መፈፀም በተለይም በደማቸው ውስጥ የኤችአይቪ ቫይረስ ላለባቸው ሴቶች እጅግ አስፈላጊ ከሚሆንበት ምክንያት አንዱ ቫይረሱ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለማድረግ ሲሆን ከፕላን ውጭ የሚደረገው ግን በጣም አደገኛና የተጸነሱትን ልጆችም ከቫይረሱ ለመጠበቅ የማያስችል የተሳሳተ አካሄድ ነው፡፡
ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከያ ዘዴን መጠቀም አቅምን ያገናዘበና ኤችአይቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ ለማድረግ እንዲሁም የእናቶችን እና የህጻናቱን ጤንነት እና ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያስችል አስተማማኝ ዘዴ ነው፡፡ ኮንዶምን መጠቀም ኢንፌክሽንን ከመተላለፍ የሚያግድ ጠቃሚው መንገድ ነው፡፡
አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት /20-43% የሚሆኑ ቫይረሱ በደማቸው ያለ እናቶች ብቻ የቤተሰብ እቅድ ዘዴን የሚጠቀሙ መሆኑ ተረጋግጦ አል፡፡ በተደረገው ጥናት ውጤት መሰረትም 14/ሚሊየን/አስራ አራት ሚሊየን የሚሆኑ ያልታ ቀዱ እርግዝናዎች በየአመቱ ከሰሀራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት ይከሰታሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያ ያዘ በተደረገው ዳሰሳ የተገኘው ምላሽ እንደሚያሳየው ከሆነ ያገቡ እና የተማሩ እንዲሁም በከ ተማ የሚኖሩ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ ሴቶች በተሻለ ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከል የሚያ ደርጉ ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ ሴቶቹ በራሳቸው ሕይወት መወሰን የማይችሉ ፤ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ (ድህነት) ያላቸው ፤ዝቅተኛ የሆነ የቤተሰብ እቅድ ዘዴ አገልግሎት ካለ እና የቤተሰብ ቁጥራቸው ከፍ እንዲል የሚፈልጉ ከሆነ ችግሩን ለማስወገድ ጥረት የማያሳዩ ናቸው፡፡
እንደውጭው አቆጣጠር በ2011/በተደረገው ጥናት በአዲስ አበባ 43.3% የሚሆኑ ቫይረሱ በደ ማቸው ያለ እናቶች ልጅ እንዲኖራቸው የሚፈልጉ ሲሆን በጥናቱ ከታቀፉት ውስጥ 71.5% የሚሆኑት በቅርብ እንደሚወልዱ ተናግረዋል፡፡ መልስ ከሰጡት 26.8% የሚሆኑት ጥናቱ በሚ ካሄድበት ወቅት እርጉዝ የነበሩ ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ በተደረገው ጥናት እንደታየው ከሆነ ሴቶች በምርመራ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ መኖሩ ሲነገራቸው ወዲያውኑ ልጅ እንዳይኖራቸው የሚወስኑ ብዙ ሲሆኑ በኬንያ ደግሞ አብዛ ኞቹ ማለትም 87% የሚሆኑት ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ እናቶች ቫይረሱ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ የሚያስችለውን ፕሮግራም በፈቃደኝነት እንደሚሳተፉና ወደፊትም ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል የቤተሰብ እቅድ ዘዴን ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን ስላሳዩ በዚህም ወደ 59% የሚደርስ ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ፈቃደኝነት እና ተግባር ታይቶ አል፡፡
በኢትዮጵያ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና በጋንዲ ሆስፒታል በውጭው አቆጣጠር በ2013/ በተደ ረገው ጥናት የታየው ያልተፈለገ እርግዝና ቫይረሱ በደማቸው ባለባቸው ሴቶች 56.3% ሲሆን ቫይረሱ በደማቸው የሌለባቸው ሴቶች ግን 29.5% ማለትም በግማሽ ያህል የቀነሰ ነበር፡፡
አስፈ ላጊውን መከላከያ ያለማግኘት ምክንያት ተደርገው የሚወሰዱት፤
በጉዳዩ ዙሪያ ማለትም ስለመከ ላከያዎቹ አገልግሎት ትንሽ ወይ ንም ጭርሱኑ እውቀት አለመኖር፤
አገልግሎቱን ለማግኘት አለመቻል ፤
በኤችአይቪ እና በቤተሰብ እቅድ ዘዴ አገልግሎት መካከል ቅንጅት አለመኖር፤
የአድሎና መገለል ፍራቻ የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ቫይረሱ በደማቸው የሚገኝ እናቶች ኮንዶምን ስላለመጠቀም የሰጡት መልስ የሚከተለውን ይመስላል፡፡
እኔ እርጉዝ ነኝ፡፡ ስለዚህ ኮንዶም መጠቀም አያስፈልገኝም፡፡
ባለቤቴ በኮንዶም መጠቀም የሚባለውን ነገር በፍጹም አይደግፈውም፡፡አይወድም፡፡
ፍቅረኛዬ ወይንም በወሲብ የምገናኘው ሰው እኔ ቫይረሱ በደሜ ውስጥ እንዳለ አያውቅም።
በኮንዶም ወሲብን መፈጸም ስሜትን ስለሚቀንስ አላደርገውም፡፡
ምክንያቱ ባይገባኝም አልወደውም፡፡
ሌሎች፡-
ኤችአይቪ ኤይድስ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ከሚረዱ መንገዶች አንዱ ያልተፈለገ እርግ ዝናን መከላከል ወይንም ተገቢውን የጊዜ እርቀት በመጠቀም ልጆችን ማፍራት እንዲሁም ምን ያህል ልጅ በቤተሰብ መወለድ አለበት የሚለውን መወሰን ነው፡፡
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጥናት እንደሚያሳየው ከሆነ በጥናቱ ከተካተቱት በደማቸው ኤችአይቪ ቫይረስ የሚገኝባቸው ሴቶች መካከል እርግዝናቸው የታቀደ መሆኑን ያረጋገጡት 113/ሲሆኑ 60/ዎቹ ግን ካለእቅድ ማርገዛቸውን ተናግረዋል፡፡ ስለባለቤቶቻቸው ኤች አይቪ መረጃ ሲመልሱም 83/የሚሆኑት ቫይረሱ በባላቸው ደም ውስጥ እንዳለ ሲመሰክሩ 34/የሚ ሆኑት ደግሞ ነጸ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን 56/የሚሆኑት ሴቶች ባላቸው ኤችአይቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ ይኑር አይኑር የሚያውቁት ነገር የለም፡፡
ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከል ከሚያስችሉ መከላከያዎች በተለይም ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቢጠቀሙ የሚመከረው ኮንዶም ነው፡፡ ይህንን በተመለከተም ቫይረሱ በደምሽ ውስጥ መኖሩ ከታወቀ በሁዋላ ኮንዶም መጠቀም ጀምረሻል ወይ ለሚለው ጥያቄ አልጠቀምም ያሉ /71/ሲሆኑ አንዳንድ ጊዜ ያሉ /55/ናቸው፡፡ በተከታታይ እጠቀማለሁ ያሉ ግን /47/ያህል ናቸው፡፡ ኮንዶምን በእርግዝናው ወቅት ትጠቀማላችሁ ወይ ለሚለው ደግሞ አዎን የሚል ምላሽ የሰጡ /45/ ሲሆኑ አልጠቀምም ያሉት ግን 126/ናቸው፡፡
ባጠቃላይም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያሉ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ባለሙያዎች ባደረጉት ጥናት መሰረት ከተገኘው ውጤት በመነሳት የደረሱበት ድምዳሜ ከቫይረሱ ነጻ የሆነ ትውልድን ለማፍራት እንዲ ቻል፤ ቫይረሱ በደማቸው ያለ ሴቶች በተገቢው መንገድ ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከል እንዲ ችሉ ፤እንዲሁም የኢንፌክሽን መተላለፍ እንዳይኖር ተገቢው ድጋፍና ክትትል እንዲሁም ምክርና አገልግሎት መስጠት ያስፈልጋል፡፡     

Read 2747 times
Administrator

Latest from Administrator