ከሳምንታት በፊት በጠባቂያቸው 119 ላፕቶፖችን የተዘረፉት የቀድሞው የዚምባቡዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ፤ አሁን ደግሞ ጉሹንጎ ሆልዲንግስ በተባለው ተቋማቸው ተቀጥሮ በሚሰራ የሂሳብ ባለሙያ 10 ሺህ ዶላር ያህል መዘረፋቸውን አፍሪካን ኒውስ ድረገጽ ዘግቧል፡፡
ፒተር ቢሂቢ የተባለውና ዝርፊያውን ፈጽሟል የተባለው የድርጅቱ ሰራተኛ፣ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት መቅረቡን የጠቆመው ዘገባው፤ በ100 ዶላር ዋስትና የተለቀቀው ግለሰቡ በመጪዎቹ ሳምንታት ተገቢው የፍርድ ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል፡፡
ይህ የዝርፊያ ወንጀል ከተፈጸመ ከቀናት በፊትም ጠባቂያቸው የነበረ አንድ የአገሪቱ ወታደር ከሮበርት ሙጋቤ 119 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን በመዝረፍ መሰወሩንና በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ያስታወሰው ዘገባው፤ ተጠርጣሪው ግን “ላፕቶፖቹን ሙጋቤ ናቸው በስጦታ መልክ የሰጡኝ” ሲል መከራከሩንና ከሰሞኑም እርግጥም ሰጥተውት እንደሆነ ራሳቸው ሙጋቤ ምስክርነት ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል።
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል