Monday, 07 May 2018 09:45

ሙጋቤ 119 ላፕቶፖችና 10 ሺህ ዶላር ተዘረፉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    ከሳምንታት በፊት በጠባቂያቸው 119 ላፕቶፖችን የተዘረፉት የቀድሞው የዚምባቡዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ፤ አሁን ደግሞ ጉሹንጎ ሆልዲንግስ በተባለው ተቋማቸው ተቀጥሮ በሚሰራ የሂሳብ ባለሙያ 10 ሺህ ዶላር ያህል መዘረፋቸውን አፍሪካን ኒውስ ድረገጽ ዘግቧል፡፡
ፒተር ቢሂቢ የተባለውና ዝርፊያውን ፈጽሟል የተባለው የድርጅቱ ሰራተኛ፣ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ባለፈው ሳምንት ፍርድ ቤት መቅረቡን የጠቆመው ዘገባው፤ በ100 ዶላር ዋስትና የተለቀቀው ግለሰቡ በመጪዎቹ ሳምንታት ተገቢው የፍርድ ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክቷል፡፡
ይህ የዝርፊያ ወንጀል ከተፈጸመ ከቀናት በፊትም ጠባቂያቸው የነበረ አንድ የአገሪቱ ወታደር ከሮበርት ሙጋቤ 119 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን በመዝረፍ መሰወሩንና በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ያስታወሰው ዘገባው፤ ተጠርጣሪው ግን “ላፕቶፖቹን ሙጋቤ ናቸው በስጦታ መልክ የሰጡኝ” ሲል መከራከሩንና ከሰሞኑም እርግጥም ሰጥተውት እንደሆነ ራሳቸው ሙጋቤ ምስክርነት ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል።

Read 1582 times