Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Sunday, 06 May 2012 14:06

የፕሬስ ነፃነትን በማፈን ኤርትራ ትመራለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከትላንት በስቲያ የተከበረውን የዓለም የፕሬስ ቀን አስመልክቶ የፕሬስ ነፃነትን የሚያፍኑ የዓለም አገራት ዝርዝር የወጣ ሲሆን ኤርትራ፣ ሰሜን ኮርያና ሶርያ የፕሬስ ነፃነትን በማፈን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን የቀዳሚነት ስፍራ ይዘዋል፡፡በሌላ በኩል በአረብ አገራት የተካሄዱ ህዝባዊ አመፆች የሰሜን አፍሪካ አምባገነኖችንና ፈላጭ ቆራጮችን ቢያስወግዱም የላቀ የሚዲያ ነፃነትን ማረጋገጥ እንዳልቻሉ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን አስታወቀ፡፡

ቱኒዚያ የዓለም የፕሬስ ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ ከትላንት በስቲያ የዩኔስኮ ዋና ሃላፊ አይሪና ቦኰቫን ተቀብላ ያስተናገደች ሲሆን ይሄም ሃላፊው ህዝባዊ አብዮቶች በተጠነሰሱባቸው ሥፍራዎች ለአራት ቀናት የሚያደርጉት ጉብኝት አካል ነው ተብሏል፡፡

መቀመጫውን ፓሪስ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ቡድን፤ አዲሱን የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ እና በስልጣን ላይ ያሉትን የግብፅ ወታደራዊ መሪዎች ጨምሮ ስድስት አዳዲስ የፕሬስ ነፃነት “አፋኞችን” ይፋ አድርጓል፡፡

የአገሪቱን ሚዲያ እግር ከወርች ጠፍረውት የነበሩት የቀድሞ የቱኒዚያ አምባገነን መሪ ቤን አሊ ከስልጣን ከተወገዱ በኋላ በርካታ አዳዲስ ህትመቶች፣ ኦንላይን የዜና ድረገፆችና የቴሌቪዥንና የሬድዮ ጣቢያዎች እንዳቆጠቆጡ አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

 

 

Read 3152 times Last modified on Sunday, 06 May 2012 14:12