Monday, 07 May 2018 09:59

የኢትዮጵያ የሂሳብ ኦሎምፒያድ ውድድር ተጠናቀቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በኢንተሌክችዋል አለም አቀፍ ት/ቤት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረውና ከ1 መቶ በላይ ት/ቤቶች የተውጣጡ 1 ሺህ ተማሪዎች የተሳተፉበት የሂሳብ ውድድር፤ አሸናፊዎችን በመሸለምና በኪነ ጥበብ ዝግጅቶች ተጠናቀቀ፡፡
ት/ቤቱ ከ1ኛ - 3ኛ የወጡ ተማሪዎችን እንደየክፍል ደረጃቸው ከ2 ሺህ እስከ 1 ሺህ ብር እና የወርቅ፣ የብርና የነሐስ ሜዳሊያ ሸልሟል፡፡ ለአሸናፊ ተማሪ ት/ቤቶችም ዘመናዊ ፕሪንተርና ኮፒ በአንድ ላይ የያዘ ማሽን በሽልማት አበርክቷል፡፡ ውድድሩ ዘንድሮ ከ6ኛ - 8ኛ ክፍል ባሉ ተማሪዎች መካከል ለስምንተኛ ጊዜ መካሄዱም ተገልጿል።
በዚህ ውድድር የግልና የመንግሥት ት/ቤቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ የሂሳብ ውድድሩን በአገር አቀፍ ደረጃ ለማካሄድ እቅድ እንደነበራቸው የት/ቤቱ የአፍሪካ ህብረት ቅርንጫፍ መምህርና ምክትል ርዕሰ መምህር አቶ ካሳሁን አስራደው ተናግረዋል፡፡ ውድድሩ በየዓመቱ መካሄዱ የተማሪዎቹን የሂሳብ ትምህርት ፍላጎትና ችሎታ ያሳድጋልም ተብሏል፡፡

Read 2289 times