በስራ ፈጠራና በካይዘን ፅንሰ ሀሳብ ላይ ተመስርተው ባሰናዷቸው መፅሐፍት የሚታወቁት ዶ/ር አቡሽ አያሌውና እንድሪስ አራጋው “የኢንተርፕረነርሺፕ ሀሁ” የተሰኘ መፅሐፍ አዘጋጅተው ለገበያ አቀረቡ፡፡ መፅሐፉ፤ “የራስህን ቢዝነስ ለመጀመር አሁኑኑ ተነስ” በሚል ከንግድ ሀሳብ ፈጠራ እስከ ንግድ ሀሳብ እቅድ አነዳደፍ ድረስ በተግባር የተዋቀረ ትምህርት ይሰጣል ተብሏል፡፡
አንድ ሰው እንዴት ውጤታማ ቢዝነስ መጀመር ይችላል፣ በፍጥነት ገበያን ሰብሮ ለመግባት ምን መደረግ አለበት፣ የቱን አይነት የንግድ ህጋዊ አመሰራረቶች ቢመርጥ ይጠቀማል በሚሉትና መሰል ጉዳዮችም ላይ ሰፊ ሃሳብና አማራጭ ያቀርባል ተብሏል፡፡ በ330 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ በ175 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና