Sunday, 13 May 2018 00:00

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ የ62 ተከሳሾች ክስ ተቋረጠ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ታዋቂውን የልብ ሃኪምና የአዲስ የልብ ህክምና ማዕከል ባለቤት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ የ62 ተከሳሾች ክስ ትናንት ማቋረጡን አስታወቀ፡፡
ከቂሊንጦ ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ የቀረበባቸውን ክስ እንዲከላከሉ በፍ/ቤት ከተበየነባቸው 38 ተከሳሾች መካከል 26ቱ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡
በእነ ማስረሻ ሰጠኝ የክስ መዝገብ ስር ከሚገኙት 38 ተከሳሾች መካከል አራቱ በሰው መግደል ወንጀል የተከሰሱ በመሆኑ ክሳቸው ባለበት እንዲቀጥል የተባለ ሲሆን ቀደም ሲል ስምንቱ ያህሉ በነፃ መሰናበታቸው ታውቋል፡፡
ቀሪዎቹ ክሳቸው የተቋረጠላቸው በተለያዩ የሽብር ወንጀሎች ተከሰው ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው ሲከታተሉ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡  

Read 7328 times