Saturday, 12 May 2018 11:48

‹‹…ተጋቢዎች…ይህንን ሞክሩ፡፡››

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ለመሆኑ ስንቶች ይሆኑ በትዳር አለመታመን የተነሳ ወደ አልሆነ አቅጣጫ እየተጉዋዙ በስነተ ዋልዶ ጤና ችግር የታወኩ? ይህንን ጥያቄ ለመመለስ እራሱን የቻለ ጥናት ቢያስፈ ልገውም በየአቅራቢያችን ግን የታዘብናቸው ብዙ ክስተቶች አሉ፡፡ በቤታቸው ውስጥ ሆነው ልጆቻቸውን ከማሳ ደግ እና ባልን ከመርዳት ውጭ ደጁን የማያውቁ በኤችአይቪ ምክንያት ለህልፈት የተ ዳረጉ ብዙዎች ናቸው። ቤተሰባቸውን ለማስተዳደር ሲሉ ጧት ማታ ከመማሰን እና ከሚስቶቻ ቸው ውጭ ሌላ ሴት የማያውቁ ብዙ ወንዶች በግብረስጋ ግንኙነት ምክንያት በሚተላለፉ በሽታ ዎች ኤችአይቪን ጨምሮ የተጠቁ ብዙዎች ናቸው።  ምናልባትም ልቅ የግብረስጋ ግንኙ ነት መፈጸም ከአመል ወይንም ከባህርይ ጋር ብቻ የሚያያዝ አለመሆኑን እና ይልቁንም በትዳር መካከል ከሚኖር አለመግባባት ወይንም ታማኝነት ማጣት በመሳሰሉት የሚከሰት መሆኑን ብዙ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ መረጃ ዎች በትክክል ይህን ያህል ቁጥር ብለው ባይገልጹም በስፋት በአለም ላይ ሪፖርት የተደረገው ግን በዚህና በመሳሰሉት ምክንያቶች 60% የሚሆኑ ወንዶችና 40% የሚሆኑ ሴቶች በትዳር ዘመናቸው ከትዳር ውጭ ከሌላ ፍቅረኛ ጋር እንደሚገናኙ (Live-  about) የተሰኘ ድረገጽ ያስነ ብባል፡፡
Mort – Ertel የተባሉ የስነ ልቡና ባለሙያ ደግሞ ትዳር ለከፋ የጤንነት፤ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ችግር ተጋልጦ ተጋቢዎችን ብቻ ሳይሆን ዙሪያውን ያሉ ቤተሰቦችን ከዚያም በላይ በህብረተ ሰብና በአገርም ላይ ችግር ከማስከተሉ በፊት ተጋቢዎች ሊያጤኑዋቸው የሚገባቸው ነገሮች አሉ ይላሉ፡፡  
የመጀመሪያው ችግርን ወደጎን መተው ነው፡፡
አንድን ትዳር ከመፍረስ ለማዳን ችግርን እንዴት መፍታት እንዳለባቸው ባለትዳሮች አስቀድ መው ሊያውቁ ይገባል። አንዳቸው ከአንዳቸው በምን አይነት መንገድ መግባባት ወይም መገናኘት እንዳለባቸው በስርአተ ጾታው ረገድም ያለውን ልዩነት ዘልቆ መመልከት ይገባል ይላሉ ባለሙያው። ይህንን ርእሰ ጉዳይ በሌላ ሙያ የተካኑ ባለሙያዎች ወይም ከሕክምና አንጻር በመመልከት ችግሩን ለመፍታት ቢሞከር እንኩዋን ትዳርን ማዳንና እንደነበረ ለመጠበቅ መፍትሔው የሚገኘው በራሳቸው በባለጉዳዮቹ እጅ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል ይላሉ የስነልቡና ባለሙያው። Mort – Ertel የቀረበላቸው የትዳር አጋሮች የህይወት ልምድ አላቸው፡፡ ታሪኩ እንደሚከተለው ነው፡፡  
‹‹….እኔና ሚስቴ ትዳራችንን የመሰረትነው አንዳችን ለአንዳችን በፍቅር ወድቀን ነው፡፡ ለፍቅራ ችን እጅግ ጥልቅ ስሜት ነበረን፡፡ በየምሽቱ ስናወራ፤ አንዳችን ለአንዳችን ያልተጠበቀ ወይንም አስደናቂ ስጦታዎችን ስንቀባበል ፤አንዳችን አንዳችንን ስናቀማጥል፤ ብቻ ባጠቃላይ አንዳችን ከአንዳችን ውጭ ምንም የምናስበው ነገር ሳይኖር በደስታ እየኖርን ነበር፡፡ እኛ በጣም የምና ስቀናና ለሌሎች ምሳሌ የምንሆን ፍቅረኞች እና ባለትዳሮች ነበርን፡፡   
ነበርን የሚለው ቃል አለምክንያት አልመጣም፡፡ የሁዋላ ሁዋላ ግን ይህንን እ…ፍ…ፍ..ያለ እንደእሳት የሚንቦገቦግ ፍቅር የሚያጠፋ ነገር ተከሰተ፡፡ ይህ ደግሞ የብዙዎችን ትዳር የሚፈ ትን መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ አንድ ልጅ ተወልዶ ገና በሳምንት እድሜው ሞተ፡፡ ከዚያም መንትያ ሴት ልጆች ወልደን እነርሱም ገና በጨቅላነት እድሜያቸው አለፉ፡፡ ከዚህ በሁዋላ ሚስቴ በእ ኔም ባይሆን እንኩዋን በጠቅላላው በተፈጠረው ነገር በጣም እየተደበረች መጣች። ይህ ደግሞ በትክክል የሚጠበቅ ነገር ሲሆን እየዋለ እያደረ ግን በእኔና በእስዋ መካከል ችግር መፍጠሩ አልቀረም፡፡ እኔም እራሴን በስራ በጣም መጥመድ እና ጊዜ እንዳይኖረኝ መጣር ጀመርኩ፡፡ ሁለታችንም በየፊናችን መሮጥ እንጂ እንደድሮው መገናኘታችንን አፍ ለአፍ ገጥሞ ማውራታ ችንን እየተውነው መጣን፡፡ እንዲ ያውም ሳንተያይ ውለን ማታ አልጋ ላይ ብቻ አንዳችን አን ዳችንን መኖራችንን የምናረጋግጥበት አጋጣሚ በዛ፡፡ ሶስት ልጆቻችንን ካጣን በሁዋላ ሁሉም ነገር የተለየ ሆነ፡፡ ምሽቱን በሙሉ ሳቅ ጨዋታ ቀርቶ ኃላፊነትን በሚጠይቁ ጉዳዮች ጥቂት ንግግር ብቻ ተተካ፡፡ ማቆላመጥ ቀርቶ በሚያናድድ መልክ መጠራራት ጀመርን፡፡ ባጠቃላይም ግንኙነታችን ጸጥታ የመላበትና ብዙም የማያገናኘን እየሆነ መጣ፡፡
በእርግጥ ሁለታችንም ሁኔታዎች አስገድደውን እንጂ ይህ እንዲሆን አልፈለግንም፡፡ ስለዚህ ትዳ ራችንን ወደነበረበት ጤናማ ሕይወት ለመመለስ ሁለታችንም አንደምንፈልግ ተግባብተናል፡፡ ግን ወደፍቅር የሚወስደውን ጉዞ በሚመለከት አንዴ እኔ ስጀምረው እስዋ ትተወዋለች፡፡ እስዋ ስትጀምረው ደግሞ እኔ ችላ እላለሁ፡፡ በዚህ መልክ እንደቆየን አንድ እርምጃ ለመውሰድ ቁር ጠኝነቱን አሳየን፡፡  
መፍትሄው ምን ሆነ?
እማኞቹ እንደሚሉት በምን መንገድ ችግሮቻችንን መፍታት እንዳለብን የቻልነውን ያህል አነበብን፡፡ የግጭት ማስወገጃ ዘዴዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል ጥረት አደረግን ይላሉ፡፡ ለምሳሌም፡-
...ውዴ…ምን ነበር ያልሽኝ…አልሰማሁሽም…እስቲ አድምጪኝ ልድገምልሽ…አንቺ ያልሽውን ተረድቼ እንደሆነ አድምጪኝ እና አረጋግጪልኝ፡፡
…የኔ ፍቅር …ተረድተኸኛል? ይሄ ነገር እኮ እንደዚህ ቢሆን ጥሩ ነበር፡፡ አይመስልህም?
…ጨመር አርገሽ ብዪ እንጂ…ትንሽ እኮ ነው የበላሽው…፤
…ይርድሀል…ይህን እስቲ ደርብበት…፤
የመሳሰሉትን የማግባቢያ እና አንዱ ለአንዱ የሚሰ ጠውን ክብርና መተሳሰብ የሚያሳዩ ድርጊቶችንና አባባሎችን ተጠቀምን፡፡ እንዲሁም ወደተለያዩ መዝናኛዎች በመሄድ ችግሮቹን ለመፍታት ሙከራ አደረግን፡፡ ነገር ግን ያነበብ ናቸው መጽ ሐፎች፤ የሄድንባቸው የምክር አገልግሎቶች ሁሉ የሚነግሩን ችግርን አለማንሳትን ሳይሆን እያነሱ መፍትሔ መፈለግ የሚል ስለሆነ ለእኛ ምንም ጥቅም አልሰጠንም። እንዲያውም ይበልጥ ያጣላን ጀመር፡፡ ድካማችን ምንም ለውጥ አላመ ጣም፡፡ የምንነጋገራቸውና የምናደርጋቸው ድርጊቶች የይምሰል ሆኑብን፡፡ ስለዚህም ሁለታችንም ከልባችን በግልጽ ለምን ለውጥ ማምጣት እንዳልተቻለ ተነጋገርን፡፡ በስተ መጨረሻም የራሳችንን ዘዴ ቀየስን፡፡ ጊዜ ወስደን ተወያየን፡፡ አንዳችን አንዳችንን አሳመንን፡፡ በቃ፡፡ እባካችሁ …ተጋቢዎች …ትዳራችሁ ችግር ገጥሞት ከሆነ …ይህንን ሞክሩ፡፡ ››ይላሉ የራሳቸውን ምስክርነት የሰጡት ባለትዳሮች፡፡
መፍትሔ ሆኖናል ያሉት የሚከተለውን ነበር፡፡ ‹‹ገጥሞን የነበረውን ችግር ምንነት ሁለታችንም ለየራሳችን በመረዳት ወደጎን አስቀመጥነው፡፡ በእነዚህ ችግሮች ዙሪያ በድጋሚ መነታረክም አልፈለግንም፡፡ ይልቁንም… ግንኙነታችን በተለየ ሁኔታ እንዲቀጥል ያለንን አቅም በሙሉ ተጠቀምን። አስቀድሞ የተፈጠረውን ችግር እያነሱ ከመታገል ወይንም አንቺ ነሽ …አንተ ነህ …እያሉ ከመነታረክ ምንም ይልቅ ምንም እንዳልተፈጠረ አድርጎ ለምን በአዲስ መልክ ኑሮአችንን አንቀጥልም ተባባልንና ተግባባን፡፡ ምክንያቱም በውስጣችን ያለውን ፍቅራ ችንን ሊያደበዝዝ የሚችል ምንም መሰረታዊ የሆነ ጉዳት አንዳችን በአንዳችን ላይ አልፈጸም ንም፡፡ ስለዚህ  አንዳንድ ለየት ያሉ መንገዶችን ተጠቀምን፡፡ ትዳራችን በአዲስ መልክ እንደገና እንዲቀጥል ለማድረግ አዳዲስ ልማዶችን ባህሪዎችን በማምጣት አንቺ ትብሽ አንተ ትብስ በመ ባባል በሚያስገርም ሁኔታ አንዳችን በአንዳችን እቅፍ ውስጥ እንደገና ወደቅን፡፡ ፍቅር እንደገና ብለን አዲሱን የትዳር ሕይወት መንገድ ተያያዝነው፡፡ ተፈጥሮ የነበረው ችግር ከእኛ ፍላጎት ውጭ እና ከአቅማችን በላይ በሆነ ምክንያት መሆኑን አምነን አንዳችን ለአንዳችን ቀና የሆነ አስተሳሰብ እንዲኖረን የቻልነውን ያህል ሞከርን። ተሳካልንም፡፡›› ብለዋል፡፡
የስነልቡና ባለሙያው Mort – Ertel የእነዚህን ተጋቢዎች ምስክርነት ይጋሩታል፡፡ ብታምኑም ባታምኑም ይላሉ ባለሙያው...ይህ ለብዙዎች ችግር ለገጠማቸው ትዳሮች እንደ በጎ ምሳሌ የሚቆጠር ነው፡፡ ሁልጊዜም ማድረግ የሚሻለው ከተፈጠሩት ችግሮች እርቆ በተቃራኒው ግን በጎ የሆነ ግንኙነትን ለመፍጠር በተፈጠረው ወይንም ባሉበት ሁኔታ ላይ በግልጽ ተነጋግሮ አቅምን ለበጎ ነገር ማዋል ነው ፡፡ይህ ከሆነ ችግሮች ይሳሳሉ፤ ትዳር ከመፍረስ ይርፋል፤ የሌሎች በትዳር መሐል የሚከሰቱ ጣልቃ ገብነቶችም ይገታሉ ብለዋል የስነልቡና ባለሙያው፡፡   ይቀጥላል፡-

Read 2288 times