በሃገሪቱ ማንነትን መሠረት አድርገው የሚፈፀሙ ኢ-ሠብአዊ ድርጊቶችና መፈናቀሎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ያሳሰበው ሠማያዊ ፓርቲ፤ መንግስት ኃላፊነቱንም እንዲወስድ የጠየቀ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በበኩሉ፤ ከቤኒሻንጉል ተፈናቅለው ለወራት በባህርዳር ተጠልለው የሚገኙ ዜጎችን ሁኔታ እመረምራለሁ ብሏል፡፡
ጥቅምት 17 ቀን 2010 ዓ.ም ከ30 ዓመታት በላይ ከኖሩበት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለጋንፎ ወረዳ የሠው ህይወት በጠፋበት ሁኔታ በሃይል የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆችን አስመልክቶ መግለጫ ያወጣው ሠማያዊ ፓርቲ፤ ማንነትን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም በደል በአስቸኳይ እንዲቆም ለመንግስት ጥሪ አቅርቧል፡፡
በህዝቡ ላይ በደል ያደረሱ፣ ግድያ የፈፀሙና ያስፈፀሙ አካላትም ተጣርተው ተገቢውን ፍርድ እንዲያገኙ የጠየቀው ፓርቲው፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተፈፀመው መፈናቀል በመንግስት ባለስልጣናት ትዕዛዝ ነው የሚል ጥርጣሬ እንዳለውና መንግስት በባለስልጣናት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡ በመንግስት ሃላፊዎች ትዕዛዝ በተደጋጋሚ ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈፀም ጥቃት አሣሣቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ያለው ፓርቲው፤ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እየተፈፀመባቸው ያሉ ማህበረሠቦችን አስፈላጊውን ከለላ በመስጠት መንግስት ከጥቃት የመከላከል ሃላፊነት አለበት ብሏል፡፡
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል