ሰምና ወርቅ ሚዲያ ኢንተርቴይመንት፤ ስድስተኛውን የኪነጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ መገናኛ ፓናሮማ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው ቫምዳስ መዝናኛ ማዕከል ያካሂዳል፡፡
በዝግጅቱ ላይ ዶ/ር ዮናስ ባህረ ጥበብ፣ የሙዚቃ ባለሙያውና ተመራማሪ ሰርጸ ፍሬስብሃት፣ ገጣሚ ትእግስት ዓለሙ፣ አርቲስት አዜብ ወርቁ (የፕሮግራሙ አማካሪ)፣ ደራሲ በሀይሉ ገ/እግዚአብሄር፣ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩምና ገጣሚ ታደለ ሲሳይ ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡
Sunday, 03 June 2018 00:00
ስድስተኛው የኪነ ጥበብ ምሽት ሐሙስ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና