Sunday, 10 June 2018 00:00

ሲንጋፖር ለትራምፕና ለኪም ስብሰባ የአየር በረራ ገደብ ታደርጋለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


    እውን የመሆኑ ጉዳይ ሲያነጋግር የሰነበተውንና በመጪው ማክሰኞ ሊካሄድ ቀን የተቆረጠለትን የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕና የሰሜን ኮርያው አቻቸው ኪም ጁን ኡን ታሪካዊ ውይይት የምታስተናግደው ሲንጋፖር፤ ውይይቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ባሉት ቀናት ለደህንነት ስትል በአየር ክልሏ በሚካሄዱ የበረራ እንቅስቃሴዎች ላይ ገደብ እንደምታደርግ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ የአቪየሽን መስሪያ ቤት ባለፈው ረቡዕ ያወጣውን መግለጫ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ የሁለቱ መሪዎች ስብሰባ በአካባቢው አገራት የጸጥታ ስጋት የፈጠረ ሲሆን ለደህንነት ሲባል በሲንጋፖር የአየር ክልል ለሶስት ቀናት ያህል የበረራ እንቅስቃሴ ገደብ መደረጉ ከእስያ ዋነኛ የአየር በረራ መስመሮች አንዱ በሆነው በዚህ አካባቢ የበረራዎች መስተጓጎል ይፈጥራል መባሉን አመልክቷል፡፡
በእነዚህ ቀናት ወደ ሲንጋፖሩ የቻንጊ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ የሚያቀኑ አውሮፕላኖች ፍጥነታቸውን እንዲቀንሱ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው የጠቆመው ዘገባው፤ የተወሰኑ የማኮብኮቢያ መስመሮችን ብቻ እንዲጠቀሙ እንደተነገራቸውና  ለጸጥታና ደህንነት ስትል በሁለቱ መሪዎች ቆይታ ህዝቡ ድርሽ የማይልባቸው በርካታ ቦታዎች መለየታቸውንም አመልክቷል፡፡

Read 2263 times