ፕላቶ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የኮንግረስ አባል የሆኑት ጆሽዋ ዳሪዬ፣ በ3.2 ሚ ዶላር ዝርፊያ ተከከስሰው የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ተዘግቧል፡፡
ባለስልጣኑ እ.ኤ.አ ከ1999 እስከ 2007 የፕላቶ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለግዛቲቱ የአካባቢ ጥበቃ የተመደበውን 3.2 ሚሊዮን ዶላር ዘርፈው፣ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በመረጋገጡ፣ የእስር ቅጣቱ እንደተጣለባቸው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይም ታራባ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት ጆሊ ናይሜ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በሙስና ተከስሰው፣ የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል