Sunday, 06 May 2012 15:06

ሠዓሊና ቀራፂ በቀለ መኮንን የቀረፀው ሐውልት ተመረቀ

Written by  መልካሙ ተክሌ (melkamutekele@gmail.com)
Rate this item
(0 votes)

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት ዳይሬክተር፤ ሠዐሊ፣ ቀራፂና ገጣሚ በቀለ መኮንን የቀረፀው ሃውልት፤ ሳር ቤት አካባቢ ባለ አደባባይ የቆመ ሲሆን  ኃውልቱ ባለፈው እሁድ ተመርቋል፡፡ የትምህርትን ጠቀሜታ የሚያጎላውንና ሴት ተማሪ ሉል ላይ ቁጭ ብላ ስታነብ የሚያሳየውን ሃውልት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ በክብር እንግድነት  መርቀውታል፡፡

በተማሪ ቅርፅ የተሰራው ሃውልት መታሰቢያነቱ ለመምህራን ነው ተብሏል፡፡ ሃውልቱን ቀድሞ የአሜሪካ ትምህርት ቤት ይባል የነበረው ኢንተርናሽናል ኮሙኒቲ ስኩል ያሰራው ሲሆን ተማሪዎቹ የሐውልቱን አረንጓዴ መስክ እንደሚንከባከቡ ታውቋል፡፡ የዲፕሎማቲክ መናኻሪያ የሆነችው አዲስ አበባ ማደግ የትምህርት ቤቱም ማደግ ነው ያሉት አምባሳደር ቡዝ፤ ሀገራቸው ለኢትዮጵያ ትምህርት እድገት ባለፉት ሦስት ዓመታት 80 ሚሊዮን ዶላር ማበርከቷን አስታውሰዋል፡፡

 

 

 

Read 1554 times Last modified on Sunday, 06 May 2012 15:12