በኢቢኤስ ቴሌቪዥን “ቴክ ቶክ” በተሰኘው ሾው አስገራሚ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስተዋወቅና በመተንተን የሚታወቀው የሰለሞን ካሳ “ግርምተ ሳይቴክ” መፅሐፍ ከትንት በስቲያ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በሸራተን ሆቴል ላሊበላ አዳራሽ ተመረቀ፡፡
መፅሐፉ ለኢትዮጵያውን እንዲያገለግል በአማርኛ የተፃፈ ሲሆን፤ የምረቃው ሥነ ስርዓት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የአይሲቲ ኤክስፖ ኢትዮጵያ 2010 የአይሲቲ ሳምንት ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነና በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የሚኒስትሩ የስራ ኃላፊዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችና ተጋባዥ እንግዶች እንደተገኙም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና