በሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይንመንት በየወሩ የሚካሄደው “ሰምና ወርቅ የኪነ ጥበብ ምሽት” የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ ፓኖራማ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው ቫምዳስ የመዝናኛ ማዕከል ይካሄዳል፡፡
በዚህ ምሽት ላይ ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ የጠብታ አምቡላንስ ባለቤት አቶ ክብረት አበበ፣ አርቲስቶቹ ተስፋዬ ማሞ፣ ሀረገወይን አሰፋ፣ ፍቃዱ ከበደ፣ አዜብ ወርቁ፣ ገጣሚ መቅደስ ጀምበሩ፣ መምህርት ዕፀገነት አበበ፣ ገጣሚዎቹ ብሩክ ሚፍታህ፣ ምኒልክ ብርሃኑና ሌሎችም በመሶብ ባህላዊ ባንድ ታጅበው ሥራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ ገልጿል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና