Wednesday, 11 July 2018 00:00

ቴስላ በ7 ቀናት 7 ሺህ የኤሌክትሪክ መኪኖችን አመረተ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የአሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን ሙስክ ያቋቋሙትና የኤሌክትሪክ መኪኖችን በማምረት የሚታወቀው ግዙፉ ኩባንያ ቴስላ በሰባት ቀናት ውስጥ 7 ሺህ መኪኖችን ማምረቱን ፉድዚላ ድረገጽ አስነብቧል፡፡
ኩባንያው በአማካይ በቀን 1 ሺህ ሞዴል 3 የኤሌክትሪክ መኪኖችን ማምረቱንና ይህም ቁጥር እጅግ ከፍተኛ ነው መባሉን የጠቆመው ዘገባው፣ አንዱ መኪና መሸጫ ዋጋ እስከ 50 ሺህ ዶላር ይደርሳል ተብሎ መነገሩንም አመልክቷል፡፡
ቴስላ በሰባት ቀናት ውስጥ ሰባት ሺህ መኪኖችን ማምረቱ በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው መስክ ግርምትን መፍጠሩን የጠቆመው ዘገባው፣ የታዋቂው የአሜሪካ የመኪና አምራች ኩባንያ ፎርድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ስቴቨን አርምስትሮንግ ግን፣ ይህ ምንም የሚገርምና የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ሲሉ የቴስላን ስኬት ማጣጣላቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የኛ ኩባንያ ፎርድ፣ ሰባት ሺህ መኪኖችን በአራት ሰዓታት ውስጥ አምርቶ የማጠናቀቅ የላቀ ብቃት አለው ብለዋል ሲልም ገልጧል፡፡ ወጪውን ለመቀነስና ትርፋማነቱን ለማሳደግ በማሰብ በቅርቡ ከአጠቃላይ ሰራተኞቹ 9 በመቶ ያህሉን መቀነሱ የተነገረለት ቴስላ፣ የሞዴል 3 መኪኖቹን በወቅቱ በማምረት ለደንበኞቹ ማድረስ አልቻለም በሚል ሲተች እንደሰነበተም ዘገባው አመለክቷል፡፡

Read 2359 times