Print this page
Saturday, 07 July 2018 11:55

በ“ዕድል ፈንታ” ላይ ውይይት ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

 ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በስነ - ፅሑፍ የኖቤል ሽልማት አሸናፊ በሆነው ጀርመናዊው ደራሲ ሔርማን ካርልሔስ “ናርሲስ ኤንድ ጎልድመንድ” በሚል በተፃፈውና በተርጓሚ ሰላምይሁን ኢዶሳ “ዕድል ፈንታ” በሚል ወደ አማርኛ በተመለሰው መፅሐፍ ላይ በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ - መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርበው “የማዕበል ጥንስስ” እና “ሰልስቱ ጣዖታት” መፃህፍት ደራሲ ያዕቆብ ብርሃኑ ሲሆን መድረኩን የሚመራው የቋንቋ መምህርና የታሪክ ባለሙያ በሆነው ሰለሞን ተሰማ ጂ. እንደሆነ አዘጋጁ ገልፆ፤ በውይይቱ ላይ ፍላጎት ያለው እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል፡፡

Read 4153 times