በደራሲ ኮሎኔል ፈቃደ ገብረየስ የተፃፈው “የአመራር ሳይንስና ጥበብ” መፅሐፍ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ አምስት ኪሎ በሚገኘው ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በምርቃቱ ላይ የአመራር ባለሙያዎች፣ ደራሲያን፣ የኪነ ጥበብ ወዳጆችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ ሲሆን በመፅሐፉ ላይ ዳሰሳና ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡
ደራሲው ከዚህ ቀደም “ስትራቴጂ” የተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡