Saturday, 28 July 2018 15:21

85% ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መኪኖች ከሃያ አመታት በላይ ያገለገሉ ናቸው ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከተለያዩ የአለማችን አገራት ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡት የተለያዩ ከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎች መካከል 85 በመቶ ያህሉ በውጭ አገራት ለ20 አመታትና ከዚያ በላይ አገልግሎት የሰጡ መሆናቸውን አንድ አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ሴንተር ፎር ሳይንስ ኤንድ ኢንቫይሮመንት የተሰኘው ተቋም ባለፈው ማክሰኞ ይፋ ባደረገው አለማቀፍ የጥናት ሪፖርት እንዳለው፣ በአሁኑ ወቅት በመላ አገሪቱ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙ ተሽከርካሪዎች መካከል አብዛኞቹ 30 አመታትና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ናቸው ተብሎ ይገመታል፡፡
በኢትዮጵያ አገልግሎት የሚሰጡ የከባድና ቀላል ተሽከርካሪዎች ቁጥር ባለፉት 15 አመታት በስድስት እጥፍ ያህል ማደጉን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ከተመረቱ ረጅም ጊዜ ያስቆጠሩ ተሽከርካሪዎች ከውጭ አገራት እንዳይገቡ የሚከልክል የዕድሜ ገደብ ህግና መመሪያ አለመኖሩንና ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሰጡ በርካታ ተሽከርካሪዎች ወደ አገሪቱ እንደሚገቡ አመልክቷል፡፡
በርካታ የአፍሪካ አገራት ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሰጡ አሮጌ መኪኖችን ካደጉት አገራት በከፍተኛ መጠን እንደሚያስገቡ የጠቆመው የተቋሙ ሪፖርት፣ ይህም የአገራቱን ዜጎች ከአካባቢ ብክለት ጋር ተያይዘው ለሚከሰቱ የጤና ችግሮችና ለመኪና አደጋዎች እየዳረገ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡

Read 3930 times