ሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት በየወሩ የሚያዘጋጀው ስምንተኛው ዙር የኪነ-ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ መገናኛ ፓኖርማ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው ቫምዳስ የመዝናኛ ማዕከል ይካሄዳል፡፡
በዚህ ምሽት ዶ/ር ሙሴ ያዕቆብ፣ የሥነ ጥበባት ተባባሪ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን፣ አርቲስቶቹ ሰለሞን ቦጋለ፣ አዜብ ወርቁ፣ ደራሲ ሕይወት እምሻው፣ ደራሲ ሄርሜላ ሰለሞን፣ መምህር ዕፀገነት ከበደ፣ ፅጌሬዳ ጎንፋ፣ እንዲሁም ገጣሚዎቹ ልዑል ሃይሌ፣ ማህሌት አፈወርቅና ሌሎችም በመሶብ ባህላዊ ባንድ ታጅበው ሥራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ዓለሙ አስታውቋል፡፡