Monday, 06 August 2018 00:00

ሁዋዌ በ3 ወራት 54.2 ሚሊዮን ሞባይሎችን ሸጧል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ሳምሰንግ በሽያጭ ሲመራ፣ አፕል ቦታውን ለሁዋዌ አስረክቧል

    ታዋቂው የቻይና ኩባንያ ሁዋዌ በአለማችን የስማርት ሞባይል ቀፎዎች ገበያ በርካታ ምርቶችን በመሸጥ በአፕል ተይዞ የቆየውን የ2ኛነት ደረጃ መረከቡን ሲኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
የቻይናው ሁዋዌ እስካለፈው ሰኔ በነበሩት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ በአለማቀፍ ደረጃ 54.2 ሚሊዮን ሞባይሎችን መሸጡንና በአለማቀፍ ገበያ ውስጥ የ15.8 በመቶ ድርሻን መያዙን የጠቆመው ዘገባው፤ የታዋቂው አይፎን አምራች የሆነው አፕል ኩባንያ በአንጻሩ 41.3 ሚሊዮን ሞባይሎችን በመሸጥ የ12.1 በመቶ የገበያ ድርሻ መያዙን አመልክቷል፡፡
የደቡብ ኮርያው ሳምሰንግ ኩባንያ በአለማቀፍ የሞባይል ሽያጭና የገበያ ድርሻ መሪነቱን ይዞ መቀጠሉን የጠቆመው ዘገባው፤ በተጠቀሱት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ 71.5 ሚሊዮን የተለያዩ አይነት የሞባይል ቀፎዎችን በመሸጥ በአለማቀፉ የሞባይል ገበያ ውስጥ የ20.9 በመቶ ድርሻውን መያዙን ገልጧል።

Read 2173 times