Tuesday, 07 August 2018 00:00

የአመቱ የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ዝነኞች ይፋ ተደረጉ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ታዋቂው ፎርብስ የ2018 የፈረንጆች አመት የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ 100 ዝነኞች ዝርዝር ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ አሜሪካዊው የከባድ ሚዛን ቦክስ ሻምፒዮናው ሜይዌዘር በ285 ሚሊዮን ዶላር ቀዳሚነቱን ይዟል፡፡
የኦስካር ተሸላሚው ታዋቂው የፊልም ተዋናይ ጆርጅ ክሉኒ ባለፉት 12 ወራት ከታክስ በፊት 239 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት የሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፣ የሪያሊቲ ሾው አዘጋጇ ኬሊ ጄኔር በ166.6 ሚሊዮን ዶላር ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
ፎርብስ ለ22ኛ ጊዜ ይፋ ባደረገው አመታዊው የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ ዝነኞች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት የዘንድሮ 100 ከዋክብት በድምሩ 6.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘታቸው የተነገረ ሲሆን፣ ዝነኞቹ ከ17 የአለማችን አገራት የተውጣጡ ናቸው ተብሏል፡፡
በዘንድሮው የፎርብስ ከፍተኛ ተከፋይ የአለማችን ዝነኞች ዝርዝር ውስጥ ከስፖርቱ ዘርፍ የተመረጡትን ክርስቲያኖ ሮናልዶና ሊዮኔል ሜሲን ጨምሮ፣ በሙዚቃ፣ በፊልም፣ በሚዲያና በሌሎች የተለያዩ መስኮች የሚታወቁ ከዋክብት መካተታቸውም ተነግሯል፡፡

Read 4874 times