Saturday, 18 August 2018 09:22

የነገሥታቱ ልደት ዛሬ ይከበራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 “ሰውኛ ፕሮዳክሽን ኢንተርቴይመንት” ከጉዞ አድዋ፣ ከኢጋ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽንና ከአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር፤ ዛሬ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ የእቴጌ ጣይቱን፣ የአፄ ምኒሊክንና የፊታውራሪ ገበየሁን ልደት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡
በዓሉ የአዲስ አበባ ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ በሚታደሙበት በእንጦጦው የአፄ ምኒልክ ቤተ መንግስት የሚከበር ሲሆን በልዩ ልዩ ኪነ ጥበባዊና ታሪካዊ ዝግጅቶች ተጀምሮ አዲስ አበባ የሚገኙ ዋና ዋና ታሪካዊ ሀውልቶችን በመጎብኘት እንደሚጠናቀቅ ያስታወቀው “ሰውኛ ፕሮዳክሽን ኢንተርቴይንመንት” ነው፡፡

Read 967 times